በኢትዮጵያ የከተማ ቱሪዝም አዲስ ምዕራፍ….!

መንግስት ባለፉት ዓመታት የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ከባህላዊ ፣ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ መዳረሻዎች ላይ፣ ዘመናዊ መዋቅሮችን እና የንግድ እንቅስቃሴዎችን ያካተተ አዲስ የኢኮኖሚ ምሰሶ በማካተት ሰፊ ሥራዎችን አከናውኗል። ይህ የስትራቴጂ ለውጥ፣ ጥንታዊ ታሪካችንን ከዘመናዊነት ጋር በማዋሃድ ሀገሪቱን ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ተመራጭ መዳረሻ በማድረግ ስኬታማ እንቅስቃሴ ተከናውነዋል። ​በከተሞች በተለይም በአዲስ አበባ የተጀመሩት ዘመናዊ የከተማ ልማት ሥራዎች የቱሪዝም ዘርፉን ገጽታ … Read more

ቱሪዝም ለሀገር እድገት ያለውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎለብቱ የገበታ መርሐ ግብሮች

በገበታ ለሸገር፣ ለሀገርና ለትውልድ መርሐ ግብሮች የተገነቡ የቱሪዝም መዳረሻዎች ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያሳድጉ ናቸው አሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፡፡ሚኒስትሯ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከአባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ÷ በየአካባቢው የሚገኙ የቱሪዝም ሀብቶችን ለማልማት በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡  መንግሥት ቱሪዝምን አንዱ የኢኮኖሚ ምሰሶ በማድረግ የመዳረሻ ልማትን ጨምሮ በርካታ … Read more

ኢትዮጵያ፡ የዓለም ቀጣዩ የቱሪዝም መናገሻ

የቀደሙ አባቶቻችን ክብር የትውልድ ኩራት ነው፡፡ የዛሬው ትጋት ደግሞ የነገው መተኪያ የሌለው ቅርስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማዕዘን፣ የሰው ዘር በኩር መገኛና የታሪክ ማኅደር መሆኗን ዓለም አውቆት፣ እኛም ደግመን ደጋግመን ተርከነው የኖርነው እውነት ነው። ሆኖም ግን “ያለፈው ታሪክ ለዛሬ ስንቅ እንጂ መኖሪያ አይሆንም” እንደሚባለው በትናንት ታሪክ ማማ ላይ ብቻ ተቀምጦ መኖር የጉዞ መዳረሻን አያሰፋም።   ዛሬ … Read more

የሳዑዲ ዓረቢያ የቱሪዝም ልዑካን ቡድኑ የኢትዮጵያ ጉብኝት በስኬት ተጠናቀቀ፤

ከሳውዲ አረቢያ የሚመጡ ቱሪስቶችን ቁጥር ለማሳደግ ያለመ የትውውቅ ጉዞ (Familiarization Trip) በቱሪዝም ሚኒስቴር፣ በሪያድ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እና ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በመተባበር ሚያዝያ 11  እስከ 15  ሲካሄድ የቀየው የሳዑዲ ዓረቢያ የቱሪዝም ልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ ቆይታ በስኬት ተጠናቋል። የጉብኝቱ ዓላማ የኢትዮጵያን አዳዲስ የቱሪስት መዳረሻዎች፣ ታሪካዊና ባህላዊ እሴቶች ለሳዑዲ ዓረቢያና ለባህረ-ሰላጤው ሀገራት እንዲሁም ለአለም ህዝብ በማስተዋወቅ … Read more

የመዲናዋ ሆቴሎች ለአፍሪካ እንግዶች የኢትዮጵያን እንግዳ ተቀባይነት የሚያንጸባርቅ መሥተንግዶ

ሆቴሎች አስፈላጊውን ዝግጅት በማጠናቀቅ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ተሳታፊ እንግዶችን መቀበል ጀምረዋል አለ የአዲስ አበባ ሆቴል ባለቤቶች ማህበር፡፡ የማህበሩ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አስቴር ሰለሞን ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ የአዲስ አበባ ሆቴሎች የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ተሳታፊ እንግዶችን የሚመጥን አገልግሎት ለመስጠት አስፈላጊውን ዝግጅት አድርገዋል። አሁን ላይም ሆቴሎች ለአፍሪካውያን እንግዶች የኢትዮጵያን የእንግዳ ተቀባይነት ባሕል በተላበሰ መልኩ አቀባበል እያደረጉ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ ሆቴሎች … Read more

ሀገራችን በዩኔስኮ ያስመዘገበቻቸው ቅርሶች 18 ደርሰዋል – የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ

የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ “ጊፋታ” በዓል በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ድርጅት ዩኔስኮ መመዝገቡን ምክንያት በማድረግ የደስታ ማብሰሪያ መርኃ ግብር በወላይታ ሶዶ ስታዲየም ተካሂዷል። በመርኃ ግብሩ ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፤ “‘ጊፋታ’ ከወላይታ ህዝብ አልፎ߹ ከኢትዮጵያም ተሻግሮ የዓለም ህዝቦች አኩሪ እሴት ሆኖ የተመዘገበ ድንቅ እሴት ነው” ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በብዝኃነት የተሟሸች፣ በህብረ ብሔራዊነት የደመቀች በታሪክ እና በተፈጥሮ … Read more

በቡና ቱሪዝም ላይ የሚመክር ሀገር አቀፍ ጉባኤ ተካሄደ::

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (JICA) ጋር በመተባበር ቡናን በሀገሪቱ የቱሪስት መዳረሻነት ማዕቀፍ ውስጥ ለማካተት የሚያስችል ሀገር አቀፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በጅማ ከተማ አካሂዷል። ይህ መድረክ በዋናነት የተበታተኑ የቡና ማስተዋወቅ ስራዎችን በቅንጅት ለመምራትና የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ ለዓለም በማስተዋወቅ ከዘርፉ የሚገኘውን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል። ​የሚኒስቴሩ የመዳረሻና የቱሪዝም ምርት ልማት ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙሳ … Read more

በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ዘርፍ እንዲሰማሩ ከኢትዮ-አሜሪካን የንግድ ምክር ቤት አባላት ብዙ ይጠበቃል፡፡

ሚኒስትሯ ከዋሽንግተን ዲ.ሲ. እና ከተለያዩ የአሜሪካን ግዛቶች የተውጣጡ የኢትዮ-አሜሪካን የንግድ ምክር ቤት አባላት በቢሯቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት እንዳሉት አሁን ያለው የኢትዮጵያ ገጽታ ለተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ምቹና ሳቢ ነው፡፡ በተለይ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መንግስት ለቱሪዝም ዘርፉ የሰጠው ትኩረት ቱሪዝሙ የኢትዮጵያን ትክክለኛ መልክ እያሳየ መሆኑን ጠቁመው የንግድ ምክርቤቱ አባላት ሀገራቸውን በአግባቡና ትክክለኛ መልኳን እንዲታወቅ ማድረግ እና ቀርበው መረጃዎችን … Read more

“ከአንኮበር እስከ ሐረር በር”፦ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የ6 ከተሞች ውድድር በደብረ ብርሃን በድምቀት ተጀመረ::

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና “ከአንኮበር እስከ ሐረር በር” በሚል መሪ ቃል ሀገርን በሩጫ ለማስተዋወቅ የታቀደው የ6 ከተሞች የሩጫ ውድድር ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ በታላቅ ድምቀት ተካሂዷል። በከተማዋ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው ታላቁ ሩጫ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን እና ከልዩ ልዩ ስፍራዎች የመጡ የሩጫ አፍቃሪዎችን ተሳትፈዋል። ​የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ውድድር የኢትዮጵያን የቱሪስት መዳረሻዎች በሩጫ አማካኝነት ለዓለም … Read more

ኢትዮጵያ  የቡና መገኛና የቡና አፈላል ስርዐት በባህላዊ መንገድ ለአለም ያስተዋወቀች ሀገር ናት፡፡

የቡና ስነስርዓት፡ ቡና ኢትዮጵያን አንድ የሚያደረግ የባህላዊ ዕሴት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ቡና አፈላል ስነስርዓት፣ እንግዳ ተቀባይነትን፣ ማህበረሰባዊ እሴትን እና ትውፊትን የሚያንፀባርቅ የዘመናት ባህል ነው።