የቱሪዝም ዘርፍ የትኩረት መስኮች
01
የቱሪስት መዳረሻ እና መሠረተ ልማት
አዳዲስ የቱሪዝም መስህቦችን ያለማል፣ ነባር የቱሪዝም መዳረሻዎች እንዲጎለብቱ እና የቱሪዝም ምርት እና አገልግሎት በዓይነትና በመጠን እንዲያድጉ በማድረግ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያደርጋል፣ የግል ባለሃብቶችም በልማቱ እንዲሳተፉ ያበረታታል፤
02
የቱሪዘም ገበያ ልማት
የተለያዩ የቱሪዝም ባለድርሻ አካላት የሚያከናውኗቸውን የቱሪዝም ገበያ ፍለጋና ማስተዋወቅ፣ የገበያ ትስስር እና ብራንዲንግ ሥራዎችን በማቀናጀትና በመምራት የአገሪቱን የቱሪዝም ሃብቶች፣ መስህቦችና መልካም ገፅታ በውጭ ሀገርና በሀገር ውስጥ በስፋት ያስተዋውቃል፤ አዳዲስ የቱሪዝም ገበያዎችን ይፈጥራል፣ የዘርፉን የገበያ ድርሻ እንዲያድግ ያደርጋል፤
03
የቱሪስት አገልግሎቶች ልህቀት
የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ደረጃዎች ይወስናል፣ ተፈጻሚነቱን ይቆጣጠራል፤
ሥልጣኑ በግልጽ በሌላ አካል ካልተሰጠ በስተቀር ከአንድ በላይ በሆኑ ክልሎች ውስጥ አገልግሎት ለሚሰጡ ወይም ህግ በሚፈቅደው አግባብ በውጭ ባለሀብቶች ለሚካሄዱ የቱሪስት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ፈቃድ ይሰጣል፣ ይቆጣጠራል፤
04
የተፈጥሮና ባህላዊ ሃብቶች ጥበቃና አጠቃቀም
የሀገሪቱ የተፈጥሮ ቅርሶች እንዲጠኑ፣ እንዲጠበቁና ለቱሪዝም አመቺ ሆነው እንዲለሙና ጥቅም ላይ እንዲውሉ የሚደረጉበትን ሁኔታ ያመቻቻል፤
05
ተቋማዊ አቅም ግንባታ
አመራርና ሰራተኞች የእውቀት ክህሎትና የአመለካከት ለውጥ በማምጣት፤ሚኒስቴር መ/ቤቱ የተጣለበትን ተቋማዊ ሃላፊነት በብቃት እንዲወጣ የሚያስችሉ በርካታ ሙያዊ ስልጠናዎችን ያዘጋጃል፡፡
ወቅታዊ ዜና

የ5ቱ ዓመታት ገፆች፦ የተፈጥሮ ፀጋን ወደ ሀገር ሀብትነት የቀየረው የኢኮ-ቱሪዝም ልማት አንጸባራቂ ስኬቶች
ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ወደር የማይገኝለት ውብ ተፈጥሮ፣ ብርቅዬ የዱር እንስሳት እና አስደናቂ የመልክዓ-ምድር ጸጋ የታደለች ምድር ናት። ሆኖም ይህ ግዙፍ እምቅ አቅም ለዘመናት በበቂ ሁኔታ ጥቅም ላይ ሳይውል ቆይቷል። ዛሬ

በኢትዮጵያ የከተማ ቱሪዝም አዲስ ምዕራፍ….!
መንግስት ባለፉት ዓመታት የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ከባህላዊ ፣ታሪካዊ እና ተፈጥሯዊ መዳረሻዎች ላይ፣ ዘመናዊ መዋቅሮችን እና የንግድ እንቅስቃሴዎችን ያካተተ አዲስ የኢኮኖሚ ምሰሶ በማካተት ሰፊ ሥራዎችን አከናውኗል። ይህ የስትራቴጂ ለውጥ፣ ጥንታዊ ታሪካችንን

ቱሪዝም ለሀገር እድገት ያለውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎለብቱ የገበታ መርሐ ግብሮች
በገበታ ለሸገር፣ ለሀገርና ለትውልድ መርሐ ግብሮች የተገነቡ የቱሪዝም መዳረሻዎች ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያሳድጉ ናቸው አሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፡፡ሚኒስትሯ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባ
በቱሪዝም ዘርፍ በቅርብ ዓመታት የተሰሩ መዳረሻዎች ለአገር ገጽታ ግንባታ ከመሆንም በላይ አለም አቀፍ የቱሪዝም መዳረሻ መሆን ችለዋል
መንግስት ባለፉት ዓመታት ለቱሪዝም ዘርፉ በሰጠው ትኩረት የሀገራችንን ጸጋዎች በመረዳት በማልማት፣ በመጠበቅና በመንከባከብ በጠቅላይ ሚኒስቴር ፕሮጅክት ብቻ ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ ለምተው በአዲስ መልክ ለጎብኚዎች ክፍት ሆነዋል