የቱሪዝም ፖሊሲ ዛሬ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸደቀ። ክብርት ሰላማዊት ካሳ

የቱሪዝም ሚኒስቴር ባለፉት ጊዜያት ቅድሚያ ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራቸው ከነበሩ ስትራቴጂክ ስራዎች መካከል 17 አመት የቆየውን የቀድሞ ቱሪዝም ፖሊሲ ማሻል ዋነኛው ነው፡፡ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ የቱሪዝም ዘርፍ ተጨባጭ ሁኔታዎችን በጥልቀት በመተንተን ጊዜውን የሚመጥን የፖሊሲ ሰነድ ተዘጋጅቶ በሚኒስትሮች ም/ቤት ፀድቋል፡፡ በፖሊሲው ዝግጅት ወቅት የክልሎችና የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ተሳትፎና ግብዓት የማይተካ ሚና ነበረው፡፡ ፖሊሲው መንግስት ለዘርፉ የሰጠውን ወሳኝ … Read more

የመዲናዋ ሆቴሎች ለአፍሪካ እንግዶች የኢትዮጵያን እንግዳ ተቀባይነት የሚያንጸባርቅ መሥተንግዶ

ሆቴሎች አስፈላጊውን ዝግጅት በማጠናቀቅ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ተሳታፊ እንግዶችን መቀበል ጀምረዋል አለ የአዲስ አበባ ሆቴል ባለቤቶች ማህበር፡፡ የማህበሩ ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አስቴር ሰለሞን ለፋና ዲጂታል እንዳሉት÷ የአዲስ አበባ ሆቴሎች የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ተሳታፊ እንግዶችን የሚመጥን አገልግሎት ለመስጠት አስፈላጊውን ዝግጅት አድርገዋል። አሁን ላይም ሆቴሎች ለአፍሪካውያን እንግዶች የኢትዮጵያን የእንግዳ ተቀባይነት ባሕል በተላበሰ መልኩ አቀባበል እያደረጉ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ ሆቴሎች … Read more

ሀገራችን በዩኔስኮ ያስመዘገበቻቸው ቅርሶች 18 ደርሰዋል – የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ

የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ “ጊፋታ” በዓል በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ድርጅት ዩኔስኮ መመዝገቡን ምክንያት በማድረግ የደስታ ማብሰሪያ መርኃ ግብር በወላይታ ሶዶ ስታዲየም ተካሂዷል። በመርኃ ግብሩ ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፤ “‘ጊፋታ’ ከወላይታ ህዝብ አልፎ߹ ከኢትዮጵያም ተሻግሮ የዓለም ህዝቦች አኩሪ እሴት ሆኖ የተመዘገበ ድንቅ እሴት ነው” ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በብዝኃነት የተሟሸች፣ በህብረ ብሔራዊነት የደመቀች በታሪክ እና በተፈጥሮ … Read more

በቡና ቱሪዝም ላይ የሚመክር ሀገር አቀፍ ጉባኤ ተካሄደ::

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (JICA) ጋር በመተባበር ቡናን በሀገሪቱ የቱሪስት መዳረሻነት ማዕቀፍ ውስጥ ለማካተት የሚያስችል ሀገር አቀፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በጅማ ከተማ አካሂዷል። ይህ መድረክ በዋናነት የተበታተኑ የቡና ማስተዋወቅ ስራዎችን በቅንጅት ለመምራትና የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ ለዓለም በማስተዋወቅ ከዘርፉ የሚገኘውን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል። ​የሚኒስቴሩ የመዳረሻና የቱሪዝም ምርት ልማት ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙሳ … Read more

በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ዘርፍ እንዲሰማሩ ከኢትዮ-አሜሪካን የንግድ ምክር ቤት አባላት ብዙ ይጠበቃል፡፡

ሚኒስትሯ ከዋሽንግተን ዲ.ሲ. እና ከተለያዩ የአሜሪካን ግዛቶች የተውጣጡ የኢትዮ-አሜሪካን የንግድ ምክር ቤት አባላት በቢሯቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት እንዳሉት አሁን ያለው የኢትዮጵያ ገጽታ ለተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ምቹና ሳቢ ነው፡፡ በተለይ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መንግስት ለቱሪዝም ዘርፉ የሰጠው ትኩረት ቱሪዝሙ የኢትዮጵያን ትክክለኛ መልክ እያሳየ መሆኑን ጠቁመው የንግድ ምክርቤቱ አባላት ሀገራቸውን በአግባቡና ትክክለኛ መልኳን እንዲታወቅ ማድረግ እና ቀርበው መረጃዎችን … Read more

“ከአንኮበር እስከ ሐረር በር”፦ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የ6 ከተሞች ውድድር በደብረ ብርሃን በድምቀት ተጀመረ::

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና “ከአንኮበር እስከ ሐረር በር” በሚል መሪ ቃል ሀገርን በሩጫ ለማስተዋወቅ የታቀደው የ6 ከተሞች የሩጫ ውድድር ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ በታላቅ ድምቀት ተካሂዷል። በከተማዋ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው ታላቁ ሩጫ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን እና ከልዩ ልዩ ስፍራዎች የመጡ የሩጫ አፍቃሪዎችን ተሳትፈዋል። ​የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ውድድር የኢትዮጵያን የቱሪስት መዳረሻዎች በሩጫ አማካኝነት ለዓለም … Read more

ኢትዮጵያ  የቡና መገኛና የቡና አፈላል ስርዐት በባህላዊ መንገድ ለአለም ያስተዋወቀች ሀገር ናት፡፡

የቡና ስነስርዓት፡ ቡና ኢትዮጵያን አንድ የሚያደረግ የባህላዊ ዕሴት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ቡና አፈላል ስነስርዓት፣ እንግዳ ተቀባይነትን፣ ማህበረሰባዊ እሴትን እና ትውፊትን የሚያንፀባርቅ የዘመናት ባህል ነው።

22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን “ትዉልድን በስነ-ምግባር ፤ ተቋምን በአስራር” በሚል መሪ ቃል ተከበረ::

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት አመራርና ስራተኞች ጋር በመሆን “ትዉልድን በስነ-ምግባር ፤ ተቋምን በአስራር” በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ያለውን 22ኛው የጸረ-ሙስና ቀን በዘርፍ ደረጃ አከበረ::

ከ40 በላይ አምባሳደሮች እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች በሀረር ጉብኝት እያደረጉ ነው።

  የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) ላይዘን ቢሮ በመተባበር ያዘጋጁት ከፍተኛ የዲፕሎማቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ልዑክ በምስራቅ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ፈርጥ በሆነችው ሀረር ከተማ ጉብኝት አድርገዋል።  ልዑካን ቡድኑ ኢትዮጵያ በዓለም ቅርስነት ባስመዘገበችው የሀረር ጀጎል ግንብ፤ ሀረርን ምቹ የቱሪስት መዳረሻ ያደረጓት የኮሪደር ልማት ስራዎች እንዲሁም በቅርቡ ተጠናቆ አገልግሎት … Read more

የኢትዮ-ሳውዲ የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ተሳታፊ ልዑካን ቤይኑና ኢኮ ሎጅን ጎበኙ!

በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ሳውዲ የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ተሳታፊዎች፣ በኢትዮጵያ ያለውን የቱሪዝም ዘርፍ ዕድሎችን በቅርበት ለመመልከት እንዲችሉ የቤይኑና ኢኮ ሎጅን ጎበኙ።   በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚንስቴር ሚንስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) እንደገለፁት የቱሪዝም ሚኒስቴር በያዘው አዲስ ስትራቴጂ መሰረት የመካከለኛው ምስራቅና ባህረ ሰላጤው ሀገራት የቱሪዝም እድሎችን በሚገባ ለመጠቀም እየሰራ እንደሆነ ገልፀው ለኢትዮ-ሳዑዲ መርሀ-ግብር ተሳታፊዎች በኢትዮጵያ ስላለው የቱሪዝም … Read more