ቱሪዝም ለሀገር እድገት ያለውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያጎለብቱ የገበታ መርሐ ግብሮች

በገበታ ለሸገር፣ ለሀገርና ለትውልድ መርሐ ግብሮች የተገነቡ የቱሪዝም መዳረሻዎች ዘርፉ ለሀገር ኢኮኖሚ የሚያበረክተውን አስተዋጽኦ ይበልጥ የሚያሳድጉ ናቸው አሉ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፡፡ሚኒስትሯ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ከአባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ÷ በየአካባቢው የሚገኙ የቱሪዝም ሀብቶችን ለማልማት በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡  መንግሥት ቱሪዝምን አንዱ የኢኮኖሚ ምሰሶ በማድረግ የመዳረሻ ልማትን ጨምሮ በርካታ … Read more

ኢትዮጵያ፡ የዓለም ቀጣዩ የቱሪዝም መናገሻ

የቀደሙ አባቶቻችን ክብር የትውልድ ኩራት ነው፡፡ የዛሬው ትጋት ደግሞ የነገው መተኪያ የሌለው ቅርስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማዕዘን፣ የሰው ዘር በኩር መገኛና የታሪክ ማኅደር መሆኗን ዓለም አውቆት፣ እኛም ደግመን ደጋግመን ተርከነው የኖርነው እውነት ነው። ሆኖም ግን “ያለፈው ታሪክ ለዛሬ ስንቅ እንጂ መኖሪያ አይሆንም” እንደሚባለው በትናንት ታሪክ ማማ ላይ ብቻ ተቀምጦ መኖር የጉዞ መዳረሻን አያሰፋም።   ዛሬ … Read more

ሀገራችን በዩኔስኮ ያስመዘገበቻቸው ቅርሶች 18 ደርሰዋል – የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ

የወላይታ ብሔር ዘመን መለወጫ “ጊፋታ” በዓል በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ድርጅት ዩኔስኮ መመዝገቡን ምክንያት በማድረግ የደስታ ማብሰሪያ መርኃ ግብር በወላይታ ሶዶ ስታዲየም ተካሂዷል። በመርኃ ግብሩ ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፤ “‘ጊፋታ’ ከወላይታ ህዝብ አልፎ߹ ከኢትዮጵያም ተሻግሮ የዓለም ህዝቦች አኩሪ እሴት ሆኖ የተመዘገበ ድንቅ እሴት ነው” ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ በብዝኃነት የተሟሸች፣ በህብረ ብሔራዊነት የደመቀች በታሪክ እና በተፈጥሮ … Read more

በቡና ቱሪዝም ላይ የሚመክር ሀገር አቀፍ ጉባኤ ተካሄደ::

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከጃፓን ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (JICA) ጋር በመተባበር ቡናን በሀገሪቱ የቱሪስት መዳረሻነት ማዕቀፍ ውስጥ ለማካተት የሚያስችል ሀገር አቀፍ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በጅማ ከተማ አካሂዷል። ይህ መድረክ በዋናነት የተበታተኑ የቡና ማስተዋወቅ ስራዎችን በቅንጅት ለመምራትና የኢትዮጵያን መልካም ገጽታ ለዓለም በማስተዋወቅ ከዘርፉ የሚገኘውን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ያለመ እንደሆነ ተገልጿል። ​የሚኒስቴሩ የመዳረሻና የቱሪዝም ምርት ልማት ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙሳ … Read more

በአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን በቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ዘርፍ እንዲሰማሩ ከኢትዮ-አሜሪካን የንግድ ምክር ቤት አባላት ብዙ ይጠበቃል፡፡

ሚኒስትሯ ከዋሽንግተን ዲ.ሲ. እና ከተለያዩ የአሜሪካን ግዛቶች የተውጣጡ የኢትዮ-አሜሪካን የንግድ ምክር ቤት አባላት በቢሯቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት እንዳሉት አሁን ያለው የኢትዮጵያ ገጽታ ለተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ምቹና ሳቢ ነው፡፡ በተለይ ባለፉት ጥቂት ዓመታት መንግስት ለቱሪዝም ዘርፉ የሰጠው ትኩረት ቱሪዝሙ የኢትዮጵያን ትክክለኛ መልክ እያሳየ መሆኑን ጠቁመው የንግድ ምክርቤቱ አባላት ሀገራቸውን በአግባቡና ትክክለኛ መልኳን እንዲታወቅ ማድረግ እና ቀርበው መረጃዎችን … Read more

“ከአንኮበር እስከ ሐረር በር”፦ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የ6 ከተሞች ውድድር በደብረ ብርሃን በድምቀት ተጀመረ::

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና “ከአንኮበር እስከ ሐረር በር” በሚል መሪ ቃል ሀገርን በሩጫ ለማስተዋወቅ የታቀደው የ6 ከተሞች የሩጫ ውድድር ዛሬ በደብረ ብርሃን ከተማ በታላቅ ድምቀት ተካሂዷል። በከተማዋ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው ታላቁ ሩጫ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን እና ከልዩ ልዩ ስፍራዎች የመጡ የሩጫ አፍቃሪዎችን ተሳትፈዋል። ​የልወቅሽ ኢትዮጵያ ክላሲክስ ውድድር የኢትዮጵያን የቱሪስት መዳረሻዎች በሩጫ አማካኝነት ለዓለም … Read more

ኢትዮጵያ  የቡና መገኛና የቡና አፈላል ስርዐት በባህላዊ መንገድ ለአለም ያስተዋወቀች ሀገር ናት፡፡

የቡና ስነስርዓት፡ ቡና ኢትዮጵያን አንድ የሚያደረግ የባህላዊ ዕሴት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ቡና አፈላል ስነስርዓት፣ እንግዳ ተቀባይነትን፣ ማህበረሰባዊ እሴትን እና ትውፊትን የሚያንፀባርቅ የዘመናት ባህል ነው።

22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን “ትዉልድን በስነ-ምግባር ፤ ተቋምን በአስራር” በሚል መሪ ቃል ተከበረ::

የቱሪዝም ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት አመራርና ስራተኞች ጋር በመሆን “ትዉልድን በስነ-ምግባር ፤ ተቋምን በአስራር” በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ያለውን 22ኛው የጸረ-ሙስና ቀን በዘርፍ ደረጃ አከበረ::

ከ40 በላይ አምባሳደሮች እና ዓለም አቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች በሀረር ጉብኝት እያደረጉ ነው።

  የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) ላይዘን ቢሮ በመተባበር ያዘጋጁት ከፍተኛ የዲፕሎማቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ልዑክ በምስራቅ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ፈርጥ በሆነችው ሀረር ከተማ ጉብኝት አድርገዋል።  ልዑካን ቡድኑ ኢትዮጵያ በዓለም ቅርስነት ባስመዘገበችው የሀረር ጀጎል ግንብ፤ ሀረርን ምቹ የቱሪስት መዳረሻ ያደረጓት የኮሪደር ልማት ስራዎች እንዲሁም በቅርቡ ተጠናቆ አገልግሎት … Read more

የኢትዮ-ሳውዲ የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ተሳታፊ ልዑካን ቤይኑና ኢኮ ሎጅን ጎበኙ!

በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ሳውዲ የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ተሳታፊዎች፣ በኢትዮጵያ ያለውን የቱሪዝም ዘርፍ ዕድሎችን በቅርበት ለመመልከት እንዲችሉ የቤይኑና ኢኮ ሎጅን ጎበኙ።   በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚንስቴር ሚንስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) እንደገለፁት የቱሪዝም ሚኒስቴር በያዘው አዲስ ስትራቴጂ መሰረት የመካከለኛው ምስራቅና ባህረ ሰላጤው ሀገራት የቱሪዝም እድሎችን በሚገባ ለመጠቀም እየሰራ እንደሆነ ገልፀው ለኢትዮ-ሳዑዲ መርሀ-ግብር ተሳታፊዎች በኢትዮጵያ ስላለው የቱሪዝም … Read more