22ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን “ትዉልድን በስነ-ምግባር ፤ ተቋምን በአስራር” በሚል መሪ ቃል ተከበረ::
የቱሪዝም ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት አመራርና ስራተኞች ጋር በመሆን “ትዉልድን በስነ-ምግባር ፤ ተቋምን በአስራር” በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ያለውን 22ኛው የጸረ-ሙስና ቀን በዘርፍ ደረጃ አከበረ::
የቱሪዝም ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት አመራርና ስራተኞች ጋር በመሆን “ትዉልድን በስነ-ምግባር ፤ ተቋምን በአስራር” በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከበረ ያለውን 22ኛው የጸረ-ሙስና ቀን በዘርፍ ደረጃ አከበረ::
የኢፌዲሪ ቱሪዝም ሚኒስቴር በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (UNESCO) ላይዘን ቢሮ በመተባበር ያዘጋጁት ከፍተኛ የዲፕሎማቶች እና የዓለም አቀፍ ተቋማት የሥራ ኃላፊዎች ልዑክ በምስራቅ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ፈርጥ በሆነችው ሀረር ከተማ ጉብኝት አድርገዋል። ልዑካን ቡድኑ ኢትዮጵያ በዓለም ቅርስነት ባስመዘገበችው የሀረር ጀጎል ግንብ፤ ሀረርን ምቹ የቱሪስት መዳረሻ ያደረጓት የኮሪደር ልማት ስራዎች እንዲሁም በቅርቡ ተጠናቆ አገልግሎት … Read more
በአዲስ አበባ ሲካሄድ የቆየው የኢትዮ-ሳውዲ የንግድና ኢንቨስትመንት ፎረም ተሳታፊዎች፣ በኢትዮጵያ ያለውን የቱሪዝም ዘርፍ ዕድሎችን በቅርበት ለመመልከት እንዲችሉ የቤይኑና ኢኮ ሎጅን ጎበኙ። በጉብኝቱ ላይ የተገኙት የቱሪዝም ሚንስቴር ሚንስትር ዴኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) እንደገለፁት የቱሪዝም ሚኒስቴር በያዘው አዲስ ስትራቴጂ መሰረት የመካከለኛው ምስራቅና ባህረ ሰላጤው ሀገራት የቱሪዝም እድሎችን በሚገባ ለመጠቀም እየሰራ እንደሆነ ገልፀው ለኢትዮ-ሳዑዲ መርሀ-ግብር ተሳታፊዎች በኢትዮጵያ ስላለው የቱሪዝም … Read more
ከኢትዮጵያ የተወሰዱ 12 ውድ ቅርሶችን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ጥናት እና ምርምር ተቋም ተረክቧል፡፡ ታዋቂው የኒውክሌር ሳይንስ ፕሮፌሰር ራሞን ቫይስ አያታቸው ከ100 ዓመታት በፊት በአዲስ አበባ የጀርመን ልዑክ በነበሩበት ጊዜ በስጦታና በግዥ አሰባስበው ያቆዩአቸውን ቅርሶች ነው በዛሬው ዕለት ለተቋሙ ያስረከቡት፡፡ በመርሐ ግብሩ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር)፣ የጀርመን ኤምባሲ ጉዳይ አስፈፃሚ … Read more
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቱሪዝም ሚኒስቴርን የመጀመሪያ ሩብ ዓመት እየገመገመ ነው።የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ ከክልል እና ከተማ አስተዳደር ቢሮዎች ጋር በጋራ በማቀድና በመገምግም ወደ ስራ መግባታቸውን በሪፖርቱ አመላክተዋል፡፡ በሩብ ዓመቱ የውጭ ቱሪስቶች ፍሰት መጠን 250,000 ለማድረስ ታቅዶ 376,615 ቱሪስቶች ሀገራችንን የጎበኙ ሲሆን፣ ካለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር … Read more
የቱሪስት አገልግሎት ብቃት ማረጋገጥና ደረጃ ምደባ ስራ አስፈፃሚ አቶ ታሪኩ ደምሴ የቱሪዝም ሚኒስቴር ከሲዳማ ክልል የባህልና ቱሪዝም ቢሮ እና ከቱሪዝም ማሰልጠኛ ተቋማ ጋር በመተባበር በሲዳማ ክልል ለሚገኙ የቱሪስት አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና በሀዋሳ ከተማ መስጠት ጀመረ። የስልጠናውን ማስጀመሪያ መልዕክት ያስተላለፉት የሲዳማ ክልል የባህል፣ ቱሪዝምና ስፖርት ምክትል ቢሮ ኃላፊ እና የቱሪዝም ዘርፍ ሀላፊ አቶ … Read more